• Call Us
  • +251467711112

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አምባሳደር የተመራ የፈረንሳይ የልኡካን ቡድንን በጽ/ቤታቸዉ ተቀብለው አነጋገሩ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አምባሳደር የተከበሩ አሌክሲስ ማሌክ (Alexis Malek) የተመራ የፈረንሳይ የልኡካን ቡድንን በጽ/ቤታቸዉ ተቀብለው አነጋግረዋል።

በዚህ ወቅትም በትምህርት ዘርፉ ላይ ስለሚኖሩ የትብብር መስኮች ዙሪያ ከክቡር አምባሳደሩ ጋር ውይይት አድርገዋል።

በተጨማሪም ሚኒስትሩ የኢትዮ-ፍሬንች ሊሴ ገብረማርያም ትምህርት ቤትን በተመለከተ Mission Laique Francaise (MLF) ፕሬዚዳንት እና ዋና ስራ አስፈጻሚ ጋር ትምህርት ቤቱን በተመለከተ በቀጣይ በጋራ በሚሰሩበት ሁኔታ ላይ ውይይት አድርገዋል።