• Call Us
  • +251467711112

የ12ኛ ክፍል የፈተና ውጤት መግለጫ አድራሻ ይፋ ሆነ

የ2016 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት እና የውጤት መግለጫ አድራሻ ይፋ ሆኗል፡፡

ተፈታኞች ውጤታቸውን በሚከተሉት የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የውጤት መግለጫ አማራጮች ከጳጉሜ 4 ቀን ከሌሊቱ 6፡00 ሰዓት ጀምሮ ማወቅ እንደሚችሉ ተገልጿል።

በዚህ መሰረት 

1. ፖርታል፡- https://result.eaes.et 

2. በቴሌግራም ቦት (Telegram Bot):- https://t.me/EAESbot 

3. በአጭር የጽሑፍ መልዕክት (SMS)፡- 6284 ላይ ‘R’ን በማስቀደም የመለያ ቁጥር በማስገባት (ምሳሌ R1234567) መልዕክት በመላክ ተፈታኞች ውጤታቸውን ማወቅ እንደሚችሉ ተገልጿል። ይህ አማራጭ ኢትዮ ቴሌኮም የሚያስከፍለው መደበኛ የSMS ክፍያ እንደሚኖረውም ተጠቅሷል።

ተፈታኞች ከውጤት መግለጫ ፖርታልና ቴሌግራም ቦት ላይ ጊዜያዊ ሰርቲፊኬት ማውረድና ማታም እንደሚችሉም የአገልግሎቱ መረጃ ያመለክታል፡፡ 

በተጨማሪም ተፈታኞች በውጤት እና ተያያዥ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ቅሬታ ካላቸው ወደ አገልግሎቱ ቢሮ በአካል መምጣት ሳያስፈልግ ከSMS በስተቀር በውጤት መግለጫ አማራጮቹ ላይ (Compliant) የሚለውን በመጫን የቅሬታቸውን ዓይነት በተዘጋጀ የቅሬታ ፎርም ላይ በትክክል በመሙላት ማቅረብ ይችላሉ ተብሏል።

አገልግሎቱ የቅሬታቸውን ምላሽ ቅሬታቸውን ባቀረቡበት ተመሳሳይ አድራሻ የሚያሳውቅ መሆኑንም አስታውቋል።